Wednesday, March 9, 2016

Youth inspiring author in the making

Zewge Abate

(Written back in 2006 at AAU as a graduate school project)

Ever since he was exposed to children’s books which his father, an English teacher, encouraged him to read, Bewketu Seyoum, 26, has been hooked on literature.

He is short, wide faced and often casually dressed with a messy beard. He often looks unbalanced perhaps because of the big bag he always carries. At face value, Bewketu does not look at all like an intellectual. His full name means something close to “achieving a height of authority for his knowledge.”

Thursday, April 21, 2011

የአበራ ለማ 'ጥሎ ማለፍ' ታሪካዊ ልቦለድ አጭር ቅኝት


-በዘውገ አባተ (ኦ.ዩ.)
እንደመግቢያ
በ411 ገጾች (አባሪ ሳይጨምር) የቀረበው “ጥሎ ማለፍ“ ታሪካዊ ልቦለድ ከደርግ የ17 ዓመታት የአገዛዝ ዘመናት የመጀመሪያዎቹን ወሳኝ 14 ዓመታትና በአመዛኙ አዲስ አበባን መቼቱ በማድረግ መጠላለፍ የበዛበትን የዘመኑን የፖለቲካ ሕይወት የሚተርክ ነው። ደራሲው በመግቢያው እንደገለጸው ታሪካዊ ልቦለዱ “ካንድ የደርግ ቋሚ ኮሚቴ አባል ከነበረ ግለሰብ ሕይወት ዙሪያ የተጠነጠነ ነው።“ (ገጽ 6) ከዚህ አልፎ ግን የታሪካዊ ልቦለዱ ማዕከል የሆነው ዳኛቸው ወረደ የዘመኑን ፖለቲካዊ ገጽታና ድባብ፥ የባለሥልጣናቱን ሥነ ልቡናዊ፥ አእምሯዊና ፖለቲካዊ ማንነት ይናገርበት ዘንድ ደራሲው ከምናቡ አንቅቶ የተጠቀመው ገጸ ባሕሪ ይሁን አለያም አንድ በሕይወት የነበረን የደርግ አባል ሰብእና በመውሰድ ታሪኩን የጥበብ ሥጋ አልብሶ፥ የጥበብ እስትንፋስ ይዝራበት (እውነቱ ይኸኛው ይመስላል) ተብራርቶ የተነገረን ነገር የለም። ነገር ግን ከላይ በጠቀስኳቸው በሁለቱም መንገድ ይሁን በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሙሉ በሙሉ የፈጠራ ውጤት በሆነ ገጸ ባህሪ በኩል ታሪካዊ ልቦለድን ማቀበል ይቻላል። ቁምነገሩ በሚነገረን ታሪክና ታሪኩ በሚወክለው ጊዜና ቦታ (መቼት) መካከል ባለው እውነተኛ ተዛምዶ ላይ ይመስለኛል።
መጽሃፉን እንዲያው በወፍ በረር ከሦስት የልቦለድ ዓላባውያን አኳያ ለመመልከት እሞክራለሁ። ‘‘ጥሎ ማለፍ‘‘ በቅርጽም ዳጎስ በይዘትም ሰፋ ብሎ የቀረበ ስራ እንደመሆኑ፣ መጽሃፉን በምልዓት ወይም በጥልቀት ለመቃኘት ጊዜውም አልነበረኝም። ድፍረቱንም አልሞክረውም። የመረጥኳቸው የመመልከቻ መነጽሮች የገጸ ባህሪ አሳሳል (ከዋናው ገጸ ባሕሪ አንጻር)፣ ታሪኩና ቋንቋው ናቸው። ከላይ በጠቀስኩት ቅደም ተከተል መሠረት እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ።

Friday, October 22, 2010

መገናኛ ተባእት

ስኬታማ ሲሆን ወንዱን ያወጡታል
'ጠንካራ ሴት አለች ከጀርባው' ይሉታል
ሴትም ደስ ይላታል ሸንጎ ሲቀባባት
'ረዳት ነሽ' ማለት ምስጢሩ ርቆባት
ቆማ እንደማትሄድ በራሷ ጎዳና
ማጀት እንድትባጅ ጥንት ተፈርዷልና
ፊት መሪ እንደማትሆን ይነግሯታል አሉ
ጋዜጠኛና ባል እየተማማሉ

ፍርደ ገምድሉ አለም አያልቅም ምጸቱ
ለልበ-ሙሉ ሴት ተዛብቶ አንደበቱ
ስኬታማ ስትሆን ሴትም በፈንታዋ
'ጠንካራ ወንድ አለ መቼም ከጀርባዋ'
ብሎ ይታበያል ወንዳወንዱ ሸንጎ

'ራሷን አትችልም' ከሚል አዘቅት ሰርጎ


Tuesday, December 22, 2009

አዲስ አመት

የዘመን ለውጥ ፍቺ ኖሮት ፈረንጅ ሲያከብረው በድምቀት
አፍሪካም ያግዘው ይዙዋል ለጥፋቱ እውነት ሲዶለት
ዘመነኛው ምእራባዊ ካባቶቹ ባየለ ርግጫ
እኛን ከኛ ጋር ሲያንጫጫ
በማያበራልን ብርሃን
በሚያሳፍረን ድርሳን
ባሸበረን ወፍራም ልሳን
እናውጃለን 'ሃፒ ኒው ይር'
አዲስ ጥፋት አዲስ አመት
በአውሮጳዊው የእብደት እለት

ሲጀመር አዲስ እቅድ
ሹል ትንፋሹ ሲያርበደብድ
ባውዛ አይደፍረው ጨለማችን ባለንበት ሲያስረግጠን
ያለነፍጥ እጅ ሲያሰጠን
አየሩ በደባ ሲጠን
ጸሃይ በምስራቅ እንዳትወጣ ተፈጥሮዋን እንድትገታ
በምእራብም እንዳትገባ ይልቁንም ልምዷን ትታ
እንድትዘልቅ ደምቃ በርታ
ጨረቃም ድርሽ እንዳትል በምስኪኖች የጠኔ አምባ
በአፍሪካዊ 'የጨዋ' ብሂል በምዕራባዊ ጭብጨባ
'አዲስ አመት እንኳን መጣሽ
ደግሞ እንዲሁ ባመት ያምጣሽ'
እያልን እናስቃለን

በእርጅናችን ምርቃት መዓት
ስልጣኔን ዕደጊ አልናት
በርቀት ሆና እያየችን
በርቀት ሆነን እያየናት፡፡

Monday, December 14, 2009

Dagnachew Worku: His Motives to Write and His Contributions to Ethiopian Literature

By Zewge Abate (A.A.U)



N.B. This is my first article published in the Ethiopian English private weekly, The Reporter, back in 2001.


Ethiopia, as a country of ancient history, has a long tradition of literature. Much of its pre-twentieth century literature is dominantly characterized by translation with a taste of originality. Moreover, Ethiopian literature took much time before dealing with the socio-politico-economic conditions that had been prevalent in the country. The country embraced Christianity during the fourth century A.D. since when Christian morality has been dominating the literary scene.


For ages, therefore, our literature had to embark on a smooth, unbroken move. In fact, the static nature of Ethiopian literature still seems to stand out against this world of dynamism. However, the twentieth century may justifiably be said to have made a move up-ward with the coming into view of some creative writers, among them Dagnachew Worku. The change he has brought forth to the realm of the country's literature is believed to be more significant than that of many writers of his time, and perhaps his contribution still remains unprecedented.

Friday, December 11, 2009

A sung hero in the shadow

December 10 - It was not a cold evening by Norwegian winter standards, six degrees. A majority of the crowd of thousands was chanting praises for the yet unseen guy who, at this point in time, might have sensed the burden of global adoration in the face of his dimensional challenges in sharp collision with meeting expectations. Hours elapsed before he made it to the balcony of Grand Hotel, an elevation from where Nobel Prize winners greet congratulating spectators. My first experience of the occasion, I cannot compare it to previous scenes although I presume that this is perhaps the biggest gathering from all walks of life standing so long as to express support and hope for change under his leadership of the United States, a nation whose decisions and doings exert a growing bearing on other nations in the ‘globalizing’ world. A significant others represented voices of concern lamenting the way he is dealing with the plights of warfare and global climate change.

Monday, December 7, 2009

Being there against all odds





I almost missed Teddy Afro's concert last week when he threw a magnificent one here in Oslo.